Tsehay Tadesse

ቢሮው ፍትሃዊ የገቢ አሰባሰብን ለማስፈን የሚያደርገው ጥረት ውጤታማነት ለማላቅ የተቋማት ቅንጅት ሊጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ ።

ጥቅምት 20 / 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ቢሮው የበጀት አመቱን የአንደኛ ሩብ አመት የተቋማትና የባለድርሻ አካላት የቅንጅታዊ ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በበጀት ዐመቱ የመጀመሪያው ሩብ አመት ያቀደውን የላቀ ገቢ አሰባሰብ ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅትና ትብብር በማጠናከር ያከናወናቸውን ተግባራት ዛሬ በጥልቀት በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል ።…

Read More

በቢሮው የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባዔ ተቋቋመ ።

ጥቅምት 15 / 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በሚሠጠው አገልግሎት እርካታን ማረጋገጥ ይቻል ዘንድ የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባዔን በዛሬው ዕለት አቋቁሟል። በዚህ የመማክርት ጉባኤ ምስረታ ላይ 50 የሚሆኑ ከንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፣ ከሲቪክ ማህበራት፣ ከንግድ ማህበረሰብ ፣ ከተገልጋይ ፣ ከባለድርሻ አካላት ሴክተር ተቋማት ፣ ከገቢዎች…

Read More

የቢሮው የህግ ተገዢነት ዘርፍ የበጀት አመቱን የሩብ አመት የዕቅድ አፈፃፀም በጥልቅ በመገምገም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀመጠ ።

ጥቅምት 05 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት አመት የታቀደውን ገቢ የታክስ ፍትሀዊነት በማረጋገጥ ፣ ከሌብነት ፣ ብልሹ አሰራሮችና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በመላቀቅ ገቢን በላቀ ደረጃ ለመሰብሰብ የተለያዩ አሰራሮችን ዘርግቶ ወደ ተግባር መግባቱ ይታወቃል የቢሮው የህግ ተገዢነት ዘርፍ የበጀት አመቱን የሩብ አመት ዕቅድ አፈፃፀሙን ዛሬ ከዳይሬክተሮች…

Read More

የቢሮው የታክስ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የገቢ እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በማካሄድ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎቹን አስቀመጠ ።

ጥቅምት 5 / 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የቢሮው የታክስ ዘርፍ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት አቅዶ ያከናወናቸውን ቁልፍ እና አበይት ተግባራት አፈፃፀሙን ገምግሟል ። የግምገማውን መድረክ የከፈቱት በቢሮው የታክስ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ግምገማው በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩትን ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ፣ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎች እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት…

Read More

የቢሮው የሞደርናይዜሽን ዘርፍና የቢሮ ፅ/ቤት በጋራ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የገቢ እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በማካሄድ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎቹን አስቀመጠ ።

ጥቅምት 5 / 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የቢሮው የሞደርናይዜሽንና የፅ/ቤት ዘርፍ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት አቅዶ ያከናወናቸውን ቁልፍ እና አበይት ተግባራት አፈፃፀሙን ገምግሟል ። የግምገማውን መድረክ የመሩት የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መሀመድ አብዱረማንና የፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ ናቸው። በውይይት መድረኩም በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩትን ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ፣…

Read More

የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች 18ኛውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን‹‹ ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጲያ ሕዳሴ›› በሚል መረ ቃል አከበሩ፡፡

ጥቅምት 3/2018ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በዛሬው ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከበረውን 18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የብሄራዊ መዝሙር በመዘመርና ቃለ መሀላ በመፈፀም ሥነ-ሥርዓት እንዲሁም በተለያዩ ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ አክብረው ውለዋል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳኔ ሱሌ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን የምናከብረው በእኛ ኢትዮጵያውያን…

Read More

የፈረንሳይ የልማት ድርጅት(AFD) ለገቢዎች ቢሮ በንብረት ታክስ (Property tax) አተገባበር ላይ ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገለፀ፡፡

መስከረም 26 ቀን 2018ዓ.ም ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት ልዑካን ቡድን ጋር በንብረት ታክስ አስተዳደር፣ የትግበራ ሂደትና ድጋፍ ላይ ውይይት አካሄደ፡፡ በውይይቱ የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ የከተማ አስተዳደሩ ባለፉት 5 ዓመታት በገቢ ዘርፉ ተጨባጭ ለውጦችን ለማስመዝገብ መቻሉን ለልዑካን ቡድኑ ገልፀዋል፡፡ በዚህም በ2010 ዓ.ም በከተማ አስተዳደደሩ…

Read More

ቢሮው የቁጥጥር ስራው በቴክኖሎጂ ማስደገፉ ስራቸውን በኃላፊነት ስሜት እንዲሰሩ ያስቻላቸው መሆኑን የመርካቶ ነጋዴዎች ገለፁ።

መስከረም 21 / 2018 የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ቢሮው የቁጥጥር ስራው በቴክኖሎጂ ማስደገፉ በታክስ ከፋዩ ሕብረተሰብ ዘንድ የፈጠሩት ስሜት በሚመለከት የመርካቶ ነጋዴዎችን አነጋግሯል። በመርካቶ በጨርቃጨርቅ ዘርፍ ላይ ተሰማሩት የሚሰሩት አቶ ዋቢ ግርግር እና አቶ አስፋው ሐይሌ እንደገለጹት እንደከተማ በከፈሉት ግብር የተሰሩ የልማት ስራዎች ሲያዩ ከፍተኛ የሆነ ደስታ የሚሰማቸው በመግለጽ…

Read More

ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የ13 ግብር ከፋዮች መዝገብ በማዘጋጀት ካቀረቡ ባለሙያዎች መካከል ከፍተኛ የገንዘብ መጠን የመንግስትን ጥቅም ለማሳጣት የሚያስችል ግድፈት ፈፅመው የተገኙ 10 የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች የሙያ ፈቃድ እንዲሰረዝ ጥያቄ ማቅረቡ ገለፀ፡፡

መስከረም 12 ቀን 2018ዓ.ም፣ አዲስ አበባ ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት የቅድመ ኦዲት ተግባር በማከናወን የመንግስትን ጥቅም በከፍተኛ ደረጃ ለመጉዳት የሚያስችል የገቢ ልዩነት የተገኘባቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ፈቃዳቸው እንዲሰረዝ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ቢሮው ይኸን ጥያቄውን ያቀረበው በታክስ አስተደደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 48 ንዑስ አንቀፅ 2(ሀ) መሰረት በዛሬው ዕለት ለኢትዮጲያ የሂሳብና…

Read More

የሐዋሳ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ልዑካን ቡድን አባላት ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለመዘርጋት እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ላይ የልምድ ልውውጥ አካሄዱ፡፡

መስከረም 10/ 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የሐዋሳ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በቢሮው በመገኘት ቢሮው የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን ቀልጣፋ ፣ ውጤታማ ፣ ከሙስና የፀዳ እና ግቡን ያሳካ እንዲሆን የዘረጋቸው አሰራሮች እና ስትራቴጂዎች ዙሪያ የልምድ ልውውጥ አካሂዷል ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ለቡድኑ የእንኳን ደህና መጣችሁ…

Read More