የቢሮው የሞደርናይዜሽን ዘርፍና የቢሮ ፅ/ቤት በጋራ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የገቢ እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በማካሄድ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎቹን አስቀመጠ ።

ጥቅምት 5 / 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

የቢሮው የሞደርናይዜሽንና የፅ/ቤት ዘርፍ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት አቅዶ ያከናወናቸውን ቁልፍ እና አበይት ተግባራት አፈፃፀሙን ገምግሟል ።

የግምገማውን መድረክ የመሩት የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መሀመድ አብዱረማንና የፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ ናቸው።

በውይይት መድረኩም በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩትን ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ፣ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎች እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ ያመላከተ እንደሆነ አብራርተዋል ።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ላይ የሚመለከታቸው የቢሮው ዳይሬክቶሬቶች ፣ የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስራ አስኪያጆችና የወረዳ ስራ አስተባባሪዎች እንዲሁም ስራ ሂደት አስተባባሪዎች ተሳትፈዋል ።

በግምገማዊ ውይይቱ ላይ ለተነሱ ሀሳቦች ከአመራሮቹ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል ።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *