ጥቅምት 5 / 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
የቢሮው የታክስ ዘርፍ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት አቅዶ ያከናወናቸውን ቁልፍ እና አበይት ተግባራት አፈፃፀሙን ገምግሟል ።
የግምገማውን መድረክ የከፈቱት በቢሮው የታክስ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ግምገማው በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩትን ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ፣ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎች እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ ያመላከተ እንደሆነ አብራርተዋል ።
መረጃን የማጥራት ስራን ማጠናቀቅ ፣ የጠራና የተደራጀ መረጃን ማጠናከር ፣ የገበያ ዋጋ ጥናትን ያማከለ የኦዲት ውሳኔ ጥራትና ሽፋንን ማሳደግ ፣ የሚወሰኑ ውሳኔዎችን ወደ ገንዘብ መቀየር ፣ የውዝፍ ዕዳን መረጃ በአግባቡ መያዝና መጠቀም እንደሚገባ ሃላፊዋ አሳስበዋል ።
በቀጣይ በአዲሱ የግብር አዋጅ መሰረት ግብር ከፋዮችን በመለየት ቫት መመዝገብ ያለባቸውን የማስገባት ፣ ኢ_ፊሊንግና ኢ_ፔመንትን ማጠናከር ፣ የኤክሳይዝ ታክስ መረጃን ማጠናከር ፣ የፕሪ ኦዲት ስራን ማስፋት ፣ ከህግ ተገዥነት ጋር በቅንጅት መስራት እንዲሁም የግብር ከፋይ መረጃን በአግባቡ መለየትና ማደራጀት እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።
በሁሉም ቅርንጫፎች እና ወረዳዎች እንደዘርፍ የሚወርዱ አሰራሮችን በወጥነት የመተግበር ስራ በመስራት እና የስራ ስነምግባርን የተላበሰ የአመራር ሚናን በማሳደግ እንደ ገቢ ሰብሳቢ ቢሮ አመራር የሚጠበቀውን ግዴታ በተሻሻለ መልኩ መወጣት እንደሚገባ ወ/ ሮ ወርቅነሽ አሳስበዋል ።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ላይ የሚመለከታቸው የቢሮው ዳይሬክቶሬቶች ፣ የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስራ አስኪያጆችና የወረዳ ስራ አስተባባሪዎች እንዲሁም ስራ ሂደት አስተባባሪዎች ተሳትፈዋል ።
በግምገማዊ ውይይቱ ላይ ለተነሱ ሀሳቦች ምላሽና ማብራሪያ ከዘርፉ ሀላፊ እና ዳይሬክቶሬቶች ተሰጥቶበታል ።