ቢሮው ከንግዱ ማህበረሰብና ከግብር ከፋዮች ጋር ተቀራርቦ በመወያየትና በመስራት በገቢው ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮች ለመፍታት በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡
ህዳር 19/3/2018ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከአዲስ አበባ ከተማ ንግድና ዘርፍ ማሀበራት ም/ቤት የቦርድ አመራሮችና ከ11ንዱም ክፍለ ከተማ የነጋዴ ተወካይ ማህበራት አመራሮች ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱም የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ከገቢዎች ቢሮ ከአገልግሎት አሰጣጥና የግብር ከፋይ መስተንግዶ፣ ከደረሰኝ ባለሙያዎች ቁጥጥርና ስነ ምግባር ፣ ከቀን ገቢ ግምት ፣ ከተሻሻለው…
