ባለፉት 5 ወራት ለግብር ከፋዮች ተገቢው አገልግሎት ባለመስጠት ኃላፊነታቸው ባልተወጡ 179 አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ።

ታህሳስ 11 /2018 ዓ.ም :አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የቢሮው ሞደርናይዜሽን ዘርፍ በበጀት ዓመቱ 5ወራት ውስጥ በ179 ሰራተኞች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መወሰዱን ገልጿል ። በቢሮው የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አብዱራህማን በዕቅድ አፈፃፀም ውይይቱ በበጀት ዓመቱ የተሰሩ ስራዎች ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሄዎች እንዲሁም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጠዋል ። አያይዘውም ከዋና መስራያ ቤት አንስቶ…

Read More

በመዲናዋ በተሽከርካሪ ጎማዎች ንግድ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ በተካሄደ የታክስ ኦፕሬሽን በ11 የንግድ ድርጅት ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲፈፅሙ የተገኙ 15 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

ታህሳስ 11 ቀን 2018ዓ.ም ፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የተሸከርካሪ ጎማ በሚሸጡ የንግድ ድርጅቶች ላይ ባካሄደው የኦፕሬሽን ተግባር ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲፈፅሙ የተገኙ 15 ግለሰቦችን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳውቋል፡፡ በዛሬው ዕለት ቢሮው ያካሄደው ድንገተኛ የኦፕሬሽን ተግባር ለረጅም ቀናት በተካሄደ ጥናት ላይ የተመሰረተ ሲሆን በቁጥጥር ስር የዋሉት…

Read More

ቢሮው ለከተማዋ ልማት የሚውል ገቢን በፍትሃዊነት ለመሰብሰብና ከግብር ከፋዩ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ከታማኝ ግብር ከፋዮች ጋር በቅንጅት የሚሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡

ታህሳስ 7 ቀን 2018ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ከ2017 የግብር ዘመን የፕላቲኒየምና የወርቅ ደረጃ ተሸላሚ ታማኝ ግብር ከፋዮች ጋር በተቋሙ እየተከናወኑ በሚገኙ የሪፎርም ተግባራት ዙሪያ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይት መድረኩ በቢሮው ፍትሀዊ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን ለማስፈንና ብልሹ አሰራርን ስርአት ለማስያዝ እየተከናወኑ የሚገኙ የሪፎርም ተግባራት እና የተገኙ ውጤቶች፣ አሁንም…

Read More

ቢሮው ከደረሰኝ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ በግብር ከፋዮች ከባለሙያዎች ስነ ምግባር ጉደለት ጋር በማያያዝ የሚቀርቡ ቅሬታዎች በተሟላ ደረጃ ለመቅረፍ የሚያስችል ቴክኖሎጂ አልምቶ ወደ ተግባር ማሸጋገሩ ተገለጸ ፡፡

ሕዳር 24 / 2018 ዓ . ም ፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በደረሰኝ ቁጥጥር ባለሙያዎች ዩኒፍርም ላይ በተገጠመ የካሜራ ቴክኖሎጂ ፣ ቢሮው ፍትሃዊ የገቢ አሰባሰብ ለመዘርጋት በቀየሳቸው አሰራሮች፣ በቅሬታ አቀራረብና አፈታት እንዲሁም በተቋሙ የሪፎርም ስራዎች ትግበራ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል ፡፡ ቢሮው ለከተማችን…

Read More

ቢሮው ከንግዱ ማህበረሰብና ከግብር ከፋዮች ጋር ተቀራርቦ በመወያየትና በመስራት በገቢው ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮች ለመፍታት በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡

ህዳር 19/3/2018ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከአዲስ አበባ ከተማ ንግድና ዘርፍ ማሀበራት ም/ቤት የቦርድ አመራሮችና ከ11ንዱም ክፍለ ከተማ የነጋዴ ተወካይ ማህበራት አመራሮች ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱም የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ከገቢዎች ቢሮ ከአገልግሎት አሰጣጥና የግብር ከፋይ መስተንግዶ፣ ከደረሰኝ ባለሙያዎች ቁጥጥርና ስነ ምግባር ፣ ከቀን ገቢ ግምት ፣ ከተሻሻለው…

Read More

በመዲናዋ ባለፉት አራት ወራት ከ5 ሺህ በላይ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የደረሰኝ ቁጥጥር በመካሄድ ከ954 ሚሊዮን ብር በላይ ደረሰኝ እንዲቆረጥ መደረጉ ተገለፀ።

ህዳር 17 ቀን፤2018፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት አራት ወራት በ5 ሺህ 203 የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪዎች ላይ የደረሰኝ ቁጥጥር ማካሄዱ ተገልፆል፡፡ የደረሰኝ ቁጥጥሩ በሁሉም የከተማዋ አቅጣጫዎች ወደ ከተማዋ በሚገቡ፣ከከተማዋ በሚወጡና በከተማዋ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ፣ሚኒባሶችና አነስተኛ ሽፍን መኪኖች ላይ ነው የተካሄደው፡፡ በዚህም ያለደረሰኝ ጭነት በመያዝ ሲንቀሳቀሱ…

Read More

በደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚካሄድ የደረሰኝ ቁጥጥር ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ።

ህዳር 14 ቀን፤2018፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በሁሉም የከተማዋ አቅጣጫዎች ወደ ከተማዋ የሚገቡ፣ከከተማዋ የሚወጡና በከተማዋ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ፣ሚኒባሶችና አነስተኛ ሽፍን መኪኖች ላይ የመኪና ኦፕሬሽን ስራዎች ማጠናከሩ ገልጿል። በዚህም ያለደረሰኝ የሚካሄዶ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የህግ ተጠያቂነት በአሸከርካሪዎች ላይ ጭምር እንዲሰፍን እያደረገ መሆኑ አሳውቋል። በአሁኑ ወቅት የደረሰኝ ቁጥጥሩ…

Read More

በተቋሙ ከብልሹ አሰራርና ሌብነት የፀዳ ፍትሃዊ አገልግሎትን መስጠት በየደረጃው ያለ አመራርና ፈፃሚ ተቀዳሚ ኃላፊነት ተገለፀ፡፡

ህዳር 15 ቀን 2018ዓ.ም ፣ አዲስ አበባ ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በዛሬው ዕለት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ፣ በሀገር አቀፍ ደግሞ ለ21ኛ ጊዜ ‹‹ትውልድን በስነ ምግባር ተቋም በአሰራር›› በሚል መሪ ቃል የፀረ ሙስና ቀንን በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡ በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ቢሮው ለከተማዋ ልማት…

Read More

የተጠያቂነት አሰራሮችን በማጠናከር የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ችግሮች መቅረፍ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡

ህዳር 3 ቀን 2018ዓ.ም ፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ ይህ የተገለጸው በዛሬው ዕለት የቢሮው የሞደርናይዜሽንና የፅ/ቤት ዘርፎች የበጀት ዓመቱን የ4 ወራት ዕቅድ አፈፃፀሞችን ከቅርንጫፍ የዘርፉ አመራሮች ጋር በገመገሙበት መድረክ ነው፡፡ በመድረኩ የቢሮው የፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ በየደረጃው ያለው አመራር ስራዎችን በአግባቡ በመምራት ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማረም በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ በተለይም ከአገልግሎት…

Read More

ቢሮው ለወረዳ ማይክሮ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት አመራሮች በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ ላይ የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠና ሰጠ።

ህዳር 1 ቀን 2018ዓም፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከኔዘርላንድ የልማት ድርጅት ጋር በመተባበር በስሩ ለሚገኙ የወረዳ ማይክሮ ቅ/ፅ/ቤት አመራሮች በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ 1395/2017 ላይ ስልጠና ሰጥቷል። የስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የቢሮው የታክስ ጉዳዮች ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ቢሮው በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች አቅም ለመገንባት የሚያስችሉ ተግባራት በተከታታይነት እያከናወነ ይገኛል…

Read More