በ2018 በጀት አመት ለመሠብሰብ የታቀደውን ገቢ ለማሳካትና የህግ ተገዢነት ስራን ለማጠናከር ወደ 24 የሚጠጉ አሰራሮችን ወደ ተግባር በማሸጋገር ተጨባጭ ውጤቶች እየታዩበት መሆኑ ተገለፀ ።

ነሐሴ 14 / 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በበጀት አመቱ የታቀደውን የከተማዋን ገቢ በአግባቡ ለመሠብሰብ አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ወደ ተግባር አስገብቶ እየሰራ ይገኛል ። ፍትሀዊ የሆነ የታክስ ( ግብር ) አሰባሰብ ስርዓት በከተማዋ ማስፈንና ይበልጥም የሚሰበሰበው ገቢ ከሌብነትና ብልሹ አሰራር የፀዳ እንዲሆን በህግ ተገዢነት ዘርፍ አሰራርን በመፈተሽ በማስተካከልና…

Read More

ለግንዛቤዎት

የግብር ከፋዩን የሂሳብ መዝገብ የሚያዘጋጁ የሂሳብ አዋቂዎች እና የውጪ ኦዲተሮች ኃላፊነት እና ሚና • የሂሳብ ባለሙያው የግብር ከፋዩ አመታዊ ግብር ለማሳወቅም ሆነ ለመደበኛ የኦዲት ስራ የሚያዘጋጀው የሂሳብ መዝገብ በቢሮው በተዘጋጀው የአሰራር ሰነድ ላይ የተመላከቱ ጉዳዮች በሚቀርበው የሂሳብ መዝገብ ውስጥ በአግባቡ ማካተቱን የማረጋገጥ ሀላፊነት አለበት፣ ለዚህ ስራ ያግዘው ዘንድ ከግብር ከፋዩ ሊቀበላቸው የሚገቡ ሰነዶችና መረጃዎችን ለይቶ…

Read More

ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የ2 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም በመገምገም የቀጣይ ወር የትኩረት አቅጣጫዎች አስቀመጠ፡፡

መስከረም 07 / 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት አመት የታክስ ፍትሀዊነት በማረጋገጥ ፣ ከሌብነት ፣ ብልሹ አሰራሮችና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በመላቀቅ ገቢን በላቀ ደረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ 24 የሚደርሱ አሰራሮች በመዘርጋት ወደ ተግባር ማሸጋገሩ ይታወቃል ፡፡ በዛሬው ዕለትም ከቅርንጫፎችና ወረዳዎች ጋር ባካሄደው የግምገማ መድረክ የበጀት ዓመቱ የ2…

Read More

ቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ተሳትፎና በአመራሮቿ ቁርጠኛነት አቋም የታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ እንዳስደሰታቸው ገለፁ፡፡

መስከረም 5/ 2015 ዓ. ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ” የህዳሴ ግድባችን የኢትዮጵያ ማንሰራራት ብስራት ነው ” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄዷል ። በውይይት መድረኩ የታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን ከፍታ ከማሳየቱ ባሻገር የብሔራዊ መግባባት እና አንድነትን የሚያሳይ መሆኑ ተገልፆል፡፡ የውይይቱን መድረክ የከፈቱት…

Read More

የልደታ ክፍለ ከተማ አነስኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ዕለታዊ ደረሰኝ ሳይዙ ልዩ ልዩ ሸቀቶች ከቦታ ቦታ ሲያዘዋውሩ በተገኙ 26 ተሸክርካሪዎች ላይ ቁጥጥር ማድረጉ ገለፀ።

ነሀሴ 26/ 2017 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ወደ ከተማዋ የሚገቡና የሚወጡ እንዲሁም በከተማዋ ከቦታ ወደ ቦታ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ለጫኑት ጭነት ህጋዊ ደረሰኝ ስለመያዛቸው ቁጥጥር የማድረግ ስራ ቀን በቀን ተጠናክሮ ቀጥሏል ። በዛሬው ዕለትም በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የልደታ ክፍለ ከተማ አነስኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በመኪናዎች…

Read More

የቢሮው የህግ ተገዢነት ዘርፍ የበጀት አመቱን የሩብ አመት የዕቅድ አፈፃፀም በጥልቅ በመገምገም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀመጠ ።

ጥቅምት 05 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት አመት የታቀደውን ገቢ የታክስ ፍትሀዊነት በማረጋገጥ ፣ ከሌብነት ፣ ብልሹ አሰራሮችና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በመላቀቅ ገቢን በላቀ ደረጃ ለመሰብሰብ የተለያዩ አሰራሮችን ዘርግቶ ወደ ተግባር መግባቱ ይታወቃል የቢሮው የህግ ተገዢነት ዘርፍ የበጀት አመቱን የሩብ አመት ዕቅድ አፈፃፀሙን ዛሬ ከዳይሬክተሮች…

Read More

የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች 18ኛውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን‹‹ ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጲያ ሕዳሴ›› በሚል መረ ቃል አከበሩ፡፡

ጥቅምት 3/2018ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በዛሬው ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከበረውን 18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የብሄራዊ መዝሙር በመዘመርና ቃለ መሀላ በመፈፀም ሥነ-ሥርዓት እንዲሁም በተለያዩ ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ አክብረው ውለዋል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳኔ ሱሌ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን የምናከብረው በእኛ ኢትዮጵያውያን…

Read More

የሐዋሳ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ልዑካን ቡድን አባላት ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለመዘርጋት እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ላይ የልምድ ልውውጥ አካሄዱ፡፡

መስከረም 10/ 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የሐዋሳ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በቢሮው በመገኘት ቢሮው የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን ቀልጣፋ ፣ ውጤታማ ፣ ከሙስና የፀዳ እና ግቡን ያሳካ እንዲሆን የዘረጋቸው አሰራሮች እና ስትራቴጂዎች ዙሪያ የልምድ ልውውጥ አካሂዷል ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ለቡድኑ የእንኳን ደህና መጣችሁ…

Read More

ያለደረሰኝ ግብይት በፈፀሙ 19 የአትክልትና ፍራፍሬ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወሰደ፡፡

ጳጉሜ 1 ቀን 2017ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ባካሄደው የደረሰኝ ቁጥጥር ያለደረሰኝ ሲገበያዩ የተገኙ 19 ግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱ ተገልፆል፡፡ የቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ የህግ ተገዥነት ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን ይልማ እንደገለፁት በዛሬው ዕለት ከለሊት…

Read More

የፈረንሳይ የልማት ድርጅት(AFD) ለገቢዎች ቢሮ በንብረት ታክስ (Property tax) አተገባበር ላይ ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገለፀ፡፡

መስከረም 26 ቀን 2018ዓ.ም ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት ልዑካን ቡድን ጋር በንብረት ታክስ አስተዳደር፣ የትግበራ ሂደትና ድጋፍ ላይ ውይይት አካሄደ፡፡ በውይይቱ የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ የከተማ አስተዳደሩ ባለፉት 5 ዓመታት በገቢ ዘርፉ ተጨባጭ ለውጦችን ለማስመዝገብ መቻሉን ለልዑካን ቡድኑ ገልፀዋል፡፡ በዚህም በ2010 ዓ.ም በከተማ አስተዳደደሩ…

Read More