ቢሮው የግብር አሰባሰብ ስርዓቱ ፍትሃዊ ለማድረግና ለሌብነትና ብልሹ አሰራር በር የከፈቱና ለውሳኔ አሰጣጥ አሻሚ የሆኑ ጉዳዮች ለመቅረፍ 24 አዳዲስ አሰራሮች በመዘርጋት ወደ ተግባር ማሸጋገሩ ተገለፀ፡፡
ነሐሴ 28 / 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት አጥንቶ ወደ ተግባር ባሸጋገራቸው 24 አሰራሮች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ በመግለጫው የቢሮው የታክስ ውሳኔ ቅሬታ ዳይሬክተር አቶ ኤርሚያስ ደጌ ቢሮው ግብር ከፋዮች በተለያዩ ጊዜያት የሚያነሷቸው የመልካም አስተዳደር፣ የሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን ለመዝጋት በየጊዜው የማሻሻያ አሰራሮችን ለግብር ከፋዩ ማሕበረሰብ…
