በመዲናዋ ባለፉት አራት ወራት ከ5 ሺህ በላይ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የደረሰኝ ቁጥጥር በመካሄድ ከ954 ሚሊዮን ብር በላይ ደረሰኝ እንዲቆረጥ መደረጉ ተገለፀ።

ህዳር 17 ቀን፤2018፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት አራት ወራት በ5 ሺህ 203 የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪዎች ላይ የደረሰኝ ቁጥጥር ማካሄዱ ተገልፆል፡፡ የደረሰኝ ቁጥጥሩ በሁሉም የከተማዋ አቅጣጫዎች ወደ ከተማዋ በሚገቡ፣ከከተማዋ በሚወጡና በከተማዋ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ፣ሚኒባሶችና አነስተኛ ሽፍን መኪኖች ላይ ነው የተካሄደው፡፡ በዚህም ያለደረሰኝ ጭነት በመያዝ ሲንቀሳቀሱ…

Read More

የተጠያቂነት አሰራሮችን በማጠናከር የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ችግሮች መቅረፍ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡

ህዳር 3 ቀን 2018ዓ.ም ፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ ይህ የተገለጸው በዛሬው ዕለት የቢሮው የሞደርናይዜሽንና የፅ/ቤት ዘርፎች የበጀት ዓመቱን የ4 ወራት ዕቅድ አፈፃፀሞችን ከቅርንጫፍ የዘርፉ አመራሮች ጋር በገመገሙበት መድረክ ነው፡፡ በመድረኩ የቢሮው የፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ በየደረጃው ያለው አመራር ስራዎችን በአግባቡ በመምራት ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማረም በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ በተለይም ከአገልግሎት…

Read More

ቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ተሳትፎና በአመራሮቿ ቁርጠኛነት አቋም የታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ እንዳስደሰታቸው ገለፁ፡፡

መስከረም 5/ 2015 ዓ. ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ” የህዳሴ ግድባችን የኢትዮጵያ ማንሰራራት ብስራት ነው ” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄዷል ። በውይይት መድረኩ የታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን ከፍታ ከማሳየቱ ባሻገር የብሔራዊ መግባባት እና አንድነትን የሚያሳይ መሆኑ ተገልፆል፡፡ የውይይቱን መድረክ የከፈቱት…

Read More

የታክስ ባለስልጣኑ ግብራቸውን አሳውቀው ያልከፈሉ ግብር ከፋዮች በቀሪዎቹ ጥቂት ቀናቶች ግብራቸውን አሳውቀው በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ማቅረቡ ተገለፀ ።

ጥቅምት 28 /2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብር አሳውቆ የመክፈያ ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ በከተማዋ ያሉ ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በሚከፍሉበት ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች በመገኘት በቀሪ ቀናት በመክፈል የግብር መክፈል ኃላፊነታቸዉን እንዲወጡ አሳሰበ ቢሮው ለግብር ከፋዮች ምቹ ፣ ቀልጣፋና ፈጣን የሆኑ አሰራሮችን ዘርግቶ ሲያስተናግድ ቢቆይም የ2017 በጀት…

Read More

የዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ባለሙያዎች ፈጣንና ጥራት ያለው መረጃ በአግባቡ በማደራጀትና ለተቋም አመራሮች በማቅረብ ትክክለኛ ውሳኔ እንዲወሰን የማድረግ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባቸው ተገለፀ፡፡

መስከረም 9 ቀን 2017ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ለቅርንጫፍ ፅ/ቤት የበጀትና ዕቅድ ክትትልና ድጋፍ የስራ ሂደቶችና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል፡፡ የስልጠና መድረኩን የከፈቱት የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በየደረጃው ያለው የእቅድ ክፍል ጥራት ያለው፣ ፈጣንና በአግባቡ የተደራጀና የተተነተነ መረጃ ለውሳኔ በማቅረብ የተቋሙ ዕቅድ እንዲሳካ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ ከትክክለኛና…

Read More

ባለፉት 5 ወራት ለግብር ከፋዮች ተገቢው አገልግሎት ባለመስጠት ኃላፊነታቸው ባልተወጡ 179 አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ።

ታህሳስ 11 /2018 ዓ.ም :አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የቢሮው ሞደርናይዜሽን ዘርፍ በበጀት ዓመቱ 5ወራት ውስጥ በ179 ሰራተኞች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መወሰዱን ገልጿል ። በቢሮው የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አብዱራህማን በዕቅድ አፈፃፀም ውይይቱ በበጀት ዓመቱ የተሰሩ ስራዎች ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሄዎች እንዲሁም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጠዋል ። አያይዘውም ከዋና መስራያ ቤት አንስቶ…

Read More

የቁጥጥር ባለሙያዎች ፍትሃዊ የገቢ አሰባሰብ ስርዓት ለመዘርጋት ቢሮው የሚያደርገው ጥረት እንዲሳካ ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የተጠናከረ የሕግ ማስከበርና የቁጥጥር ሾል ፍትሃዊነት ላይ በማተኮር የሚተገበር መሆኑን ነው በዛሬው ዕለት ከቁጥጥር ሰራተኞች ውይይት በተካሄደበት ወቅት የተገለፀው። በመድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በ2017 በጀት አመት ከገቢ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸው ገልፀዋል። በበጀት á‹“áˆ˜á‰ą ለተመዘገው ውጤትም በየደረጃው የሚገኘው አመራርና ፈጻሚ ተቀናጅቶ መስራት ከፍተኛ…

Read More

ቢሮው በቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ስራ መስራቱ ሕጋዊውና ሕገወጡን በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሆኑን ያነጋገርናቸው ነጋዴዎች ገለጹ ፡፡

ነሐሴ 13 / 2017 ዓ / ም የአዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የቁጥጥር ስራው በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ ማድረጉ ሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን ከመከላከልና የአሰራር ግልጽነት ከመፍጠሩም ባሻገር ሕጋዊውና ሕገወጡን በቀላሉ መለየት የሚያስችል በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በመርካቶ በመደብራቸው ሲሰሊ ያገኘናቸው ነጋዴዎች ገለጹ ፡፡ የዝግጅት ክፍላችን በመርካቶ አካባቢ በመዘዋወር ቢሮው ወደ ተግባር ባሸጋገር…

Read More

የከተማዋ ገቢ ከለውጡ ወዲህ በየዓመቱ ፈጣን እና እመርታዊ ዕድገት ማሳየቱ ተገለፀ ።

ጳጉሜ 03 / 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የነዋሪዋ የልማት ፍላጎትና የከተማዋ ፈጣን ዕድገት ከለውጡ ወዲህ ከአመት አመት በመጨመሩ በገቢ አሰባሰቡ ከፍተኛ እምርታ መምጣቱ ተገለፀ ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የህግ ተገዢነት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ሚኪያስ ሙሉጌታ ከቢሮው የኮሙንኬሽን ዳይሬክቶሬት ዝግጅት ክፍል የጳጉሜን 3 ” እምርታ ለዘላቂ ከፍታ ” በሚል…

Read More

የልደታ ክፍለ ከተማ አነስኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ዕለታዊ ደረሰኝ ሳይዙ ልዩ ልዩ ሸቀቶች ከቦታ ቦታ ሲያዘዋውሩ በተገኙ 26 ተሸክርካሪዎች ላይ ቁጥጥር ማድረጉ ገለፀ።

ነሀሴ 26/ 2017 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ወደ ከተማዋ የሚገቡና የሚወጡ እንዲሁም በከተማዋ ከቦታ ወደ ቦታ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ለጫኑት ጭነት ህጋዊ ደረሰኝ ስለመያዛቸው ቁጥጥር የማድረግ ሾል ቀን በቀን ተጠናክሮ ቀጥሏል ። በዛሬው ዕለትም በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የልደታ ክፍለ ከተማ አነስኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በመኪናዎች…

Read More