የፈረንሳይ የልማት ድርጅት(AFD) ለገቢዎች ቢሮ በንብረት ታክስ (Property tax) አተገባበር ላይ ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገለፀ፡፡

መስከረም 26 ቀን 2018ዓ.ም ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት ልዑካን ቡድን ጋር በንብረት ታክስ አስተዳደር፣ የትግበራ ሂደትና ድጋፍ ላይ ውይይት አካሄደ፡፡ በውይይቱ የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ የከተማ አስተዳደሩ ባለፉት 5 ዓመታት በገቢ ዘርፉ ተጨባጭ ለውጦችን ለማስመዝገብ መቻሉን ለልዑካን ቡድኑ ገልፀዋል፡፡ በዚህም በ2010 ዓ.ም በከተማ አስተዳደደሩ…

Read More

ባለፉት 5 ወራት ለግብር ከፋዮች ተገቢው አገልግሎት ባለመስጠት ኃላፊነታቸው ባልተወጡ 179 አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ።

ታህሳስ 11 /2018 ዓ.ም :አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የቢሮው ሞደርናይዜሽን ዘርፍ በበጀት ዓመቱ 5ወራት ውስጥ በ179 ሰራተኞች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መወሰዱን ገልጿል ። በቢሮው የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አብዱራህማን በዕቅድ አፈፃፀም ውይይቱ በበጀት ዓመቱ የተሰሩ ስራዎች ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሄዎች እንዲሁም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጠዋል ። አያይዘውም ከዋና መስራያ ቤት አንስቶ…

Read More

ቢሮው ፍትሃዊ የገቢ አሰባሰብን ለማስፈን የሚያደርገው ጥረት ውጤታማነት ለማላቅ የተቋማት ቅንጅት ሊጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ ።

ጥቅምት 20 / 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ቢሮው የበጀት አመቱን የአንደኛ ሩብ አመት የተቋማትና የባለድርሻ አካላት የቅንጅታዊ ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በበጀት ዐመቱ የመጀመሪያው ሩብ አመት ያቀደውን የላቀ ገቢ አሰባሰብ ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅትና ትብብር በማጠናከር ያከናወናቸውን ተግባራት ዛሬ በጥልቀት በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል ።…

Read More

የታክስ ባለስልጣኑ ግብራቸውን አሳውቀው ያልከፈሉ ግብር ከፋዮች በቀሪዎቹ ጥቂት ቀናቶች ግብራቸውን አሳውቀው በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ማቅረቡ ተገለፀ ።

ጥቅምት 28 /2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብር አሳውቆ የመክፈያ ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ በከተማዋ ያሉ ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በሚከፍሉበት ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች በመገኘት በቀሪ ቀናት በመክፈል የግብር መክፈል ኃላፊነታቸዉን እንዲወጡ አሳሰበ ቢሮው ለግብር ከፋዮች ምቹ ፣ ቀልጣፋና ፈጣን የሆኑ አሰራሮችን ዘርግቶ ሲያስተናግድ ቢቆይም የ2017 በጀት…

Read More

ያለደረሰኝ ግብይት በፈፀሙ 19 የአትክልትና ፍራፍሬ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወሰደ፡፡

ጳጉሜ 1 ቀን 2017ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ባካሄደው የደረሰኝ ቁጥጥር ያለደረሰኝ ሲገበያዩ የተገኙ 19 ግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱ ተገልፆል፡፡ የቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ የህግ ተገዥነት ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን ይልማ እንደገለፁት በዛሬው ዕለት ከለሊት…

Read More

በመዲናዋ ባለፉት አራት ወራት ከ5 ሺህ በላይ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የደረሰኝ ቁጥጥር በመካሄድ ከ954 ሚሊዮን ብር በላይ ደረሰኝ እንዲቆረጥ መደረጉ ተገለፀ።

ህዳር 17 ቀን፤2018፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት አራት ወራት በ5 ሺህ 203 የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪዎች ላይ የደረሰኝ ቁጥጥር ማካሄዱ ተገልፆል፡፡ የደረሰኝ ቁጥጥሩ በሁሉም የከተማዋ አቅጣጫዎች ወደ ከተማዋ በሚገቡ፣ከከተማዋ በሚወጡና በከተማዋ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ፣ሚኒባሶችና አነስተኛ ሽፍን መኪኖች ላይ ነው የተካሄደው፡፡ በዚህም ያለደረሰኝ ጭነት በመያዝ ሲንቀሳቀሱ…

Read More

የሐዋሳ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ልዑካን ቡድን አባላት ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለመዘርጋት እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ላይ የልምድ ልውውጥ አካሄዱ፡፡

መስከረም 10/ 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የሐዋሳ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በቢሮው በመገኘት ቢሮው የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን ቀልጣፋ ፣ ውጤታማ ፣ ከሙስና የፀዳ እና ግቡን ያሳካ እንዲሆን የዘረጋቸው አሰራሮች እና ስትራቴጂዎች ዙሪያ የልምድ ልውውጥ አካሂዷል ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ለቡድኑ የእንኳን ደህና መጣችሁ…

Read More

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር ችግኝ ተከላ አካሄደ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር ችግኝ ተከላ አካሄደ። ሐምሌ 24-2017 ዓ /ም የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ መርሐግብሩ የተካሄደው በአዲስ ከተማና በለሚኩራ ክፍለ ከተሞች ሲሆን በመርሐግብሩ የቢሮው ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀንበር 700 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል…

Read More

ቢሮው ለከተማዋ ልማት የሚውል ገቢን በፍትሃዊነት ለመሰብሰብና ከግብር ከፋዩ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ከታማኝ ግብር ከፋዮች ጋር በቅንጅት የሚሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡

ታህሳስ 7 ቀን 2018ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ከ2017 የግብር ዘመን የፕላቲኒየምና የወርቅ ደረጃ ተሸላሚ ታማኝ ግብር ከፋዮች ጋር በተቋሙ እየተከናወኑ በሚገኙ የሪፎርም ተግባራት ዙሪያ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይት መድረኩ በቢሮው ፍትሀዊ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን ለማስፈንና ብልሹ አሰራርን ስርአት ለማስያዝ እየተከናወኑ የሚገኙ የሪፎርም ተግባራት እና የተገኙ ውጤቶች፣ አሁንም…

Read More

“ወደ ከተማ የሚገቡ ፣የሚወጡ እንዲሁም ከተማ ውስጥ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ማንኛውም ደረቅ ጭነትና የተለያዩ ሸቀጣ ሸቀጦች የጫኑ ተሽከርካሪዎች ደረሰኝ ስለመያዛቸው ቁጥጥር እያደረግን ነው”- ገቢዎች ቢሮ

ነሀሴ 24 ቀን 2017ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በሁሉም የከተማዋ አቅጣጫዎች ወደከተማዋ የሚገቡ፣ከከተማዋ የሚወጡና በከተማዋ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ፣ሚኒባሶችና ኣነስተኛ ሽፍን መኪኖች ላይ የመኪና ኦፕሬሽን ስራዎች እያከናወነ መሆኑን አሳውቋል። ቢሮው እያካሄደ ያለው የመኪና ኦፕሬሽን ስራ ተሽከርካሪዎቹ ጭነው የሚንቀሳቀሱት ልዩ ልዩ ሸቀጦች፣ምርቶችና የኮንስትራክሽን ግብአቶች በህጋዊ ግብይት በደረሰኝ የተፈፀሙ ስለመሆናቸው…

Read More