በአዲስ አበባ በኮንስትራክሽን ግብአት አከፋፋይ ነጋዴዎች ላይ በተካሄደ የታክስ ኦፕሬሽን ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲፈፅሙ የተገኙ 11 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡

ጥር 9 ቀን 2018ዓ.ም ፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የግብር ስወራን ለመከላከልና የንግድ ሥርዓቱን ፍትሀዊነት ለማረጋገጥና የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተከናወነ የተጠና፣ የተቀናጀና ድንገተኛ ኦፕሬሽን ደረሰኝ ሳይቆርጡ ግብይት ሲፈጽሙ የተገኙ 11 የኮንስትራክሽ ግብአቶችን በማከፋፈል ንግድ ላይ የተሰማሩ ተጠርጣሪዎችን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳወቀ። ቢሮው አርብ ጥር 8 ቀን 2018ዓ.ም መርካቶን…

Read More

ቢሮው ከደረሰኝ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ በግብር ከፋዮች ከባለሙያዎች ስነ ምግባር ጉደለት ጋር በማያያዝ የሚቀርቡ ቅሬታዎች በተሟላ ደረጃ ለመቅረፍ የሚያስችል ቴክኖሎጂ አልምቶ ወደ ተግባር ማሸጋገሩ ተገለጸ ፡፡

ሕዳር 24 / 2018 ዓ . ም ፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በደረሰኝ ቁጥጥር ባለሙያዎች ዩኒፍርም ላይ በተገጠመ የካሜራ ቴክኖሎጂ ፣ ቢሮው ፍትሃዊ የገቢ አሰባሰብ ለመዘርጋት በቀየሳቸው አሰራሮች፣ በቅሬታ አቀራረብና አፈታት እንዲሁም በተቋሙ የሪፎርም ስራዎች ትግበራ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል ፡፡ ቢሮው ለከተማችን…

Read More

በመዲናዋ በተሽከርካሪ ጎማዎች ንግድ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ በተካሄደ የታክስ ኦፕሬሽን በ11 የንግድ ድርጅት ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲፈፅሙ የተገኙ 15 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

ታህሳስ 11 ቀን 2018ዓ.ም ፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የተሸከርካሪ ጎማ በሚሸጡ የንግድ ድርጅቶች ላይ ባካሄደው የኦፕሬሽን ተግባር ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲፈፅሙ የተገኙ 15 ግለሰቦችን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳውቋል፡፡ በዛሬው ዕለት ቢሮው ያካሄደው ድንገተኛ የኦፕሬሽን ተግባር ለረጅም ቀናት በተካሄደ ጥናት ላይ የተመሰረተ ሲሆን በቁጥጥር ስር የዋሉት…

Read More

በሞደርናይዜሽን ዘርፍ ወደተግባር በተሸጋገሩ አሰራሮች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

በሞደርናይዜሽን ዘርፍ ወደተግባር በተሸጋገሩ አሰራሮች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ። የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 የታቀደ የ256 ቢሊዮን ብር የገቢ ዕቅድ ለማሳካት 24 የሚደርሱ አሰራሮች ወደ ተግባር ማሸጋገሩ ይታወቃል። ቢሮው በየደረጃው የሚገኙ የሞደርናይዜሽንና ኮርፖሬት ዘርፍ እና ተጠሪነታቸው ለጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑ አመራሮች እንደሞደርናይዜሽንና ኮርፖሬት ዘርፍ በተሻሻሉ 3 አሰራሮች ዙሪያ…

Read More

በተቋሙ በየደረጃው ያለው አመራርና ፈፃሚ ኃላፊነቱን በአግባቡ በመወጣት የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች ለመቅረፍ በትኩረት መስራት እንዳለበት ተገለጸ፡፡

ጥቅምት 22 ቀን 2018ዓ.ም፣ አዲስ አበባ ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በማዕከል፣ በሁሉም ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶችና ወረዳዎች ከሚገኙ አመራሮችና ፈፃሚዎች ጋር በአገልግሎት አሰጣጥ የሚስተዋሉ ችግሮች ለመቅረፍ የሚያስችል የውይይት መድረክ በማዕከልና በሁሉም ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶቹ አካሄደ፡፡ በውይይት መድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ተቋሙ ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት በማስፈን ተልዕኮውን በአግባቡ ለመወጣት አዳዲስ አሰራሮችንና…

Read More

በመዲናዋ በኤሌክትሮኒከስ ንግድ ላይ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ በተካሄደ የታክስ ኦፕሬሽን በ6 የንግድ ድርጅ

ታህሳስ 25 ቀን 2018ዓ.ም ፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የግብር ስወራን ለመከላከልና የንግድ ሥርዓቱን ፍትሀዊነት ለማረጋገጥና የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተሰራ የተቀናጀና ድንገተኛ ኦፕሬሽን፣ ደረሰኝ ሳይቆርጡ ግብይት ሲፈጽሙ የተገኙ 6 ድርጅቶችንና 9 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዋለ። ቢሮው በዛሬው ዕለት መርካቶን ጨምሮ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በሚሸጡ የንግድ ድርጅቶች ላይ…

Read More

ዜና ትንታኔ

========= በገቢ አሰባሰቡ ላይ የታየው ሁሉን አቀፍ እድገትና እምርታ በቀጣይም በ2018 በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ፡፡ ጳጉሜ 03 / 2017 ዓ / ም ፣ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የከተማው ማህበረሰብ የመልማት ፍላጎት የመመለስ ትልቅ ኃላፊነት ወስዶ እየተጋ የሚገኝ ተቋም ነው ፡፡ በዚህም ምክንያት ቢሮው እያከናወናቸው በሚገኙ ተግባራት የተነሳ የገቢ…

Read More

በቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ በፊት ከሚደርስባቸው ማጭበርበር እንደታደጋቸው በመርካቶ ያነጋገርናቸው ግብር ከፋዮች አሳወቁ ።

ነሐሴ 12 / 2017 ዓ / ም የአዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የቁጥጥር ስራው በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በማድረግ ወደ ተግባር ማሸጋገሩ ይታወቃል ። የኮሙንኬሽን የዝግጅት ክፍላችን በመርካቶ አካባቢ ዛሬም በመዘዋወር ቢሮው ወደ ተግባር ባሸጋገረው በቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ስርዓት ላይ ያለውን ሂደት የታክስ ( ግብር ) ከፋዮች አስተያየት ቅኝት አድርጓል ፡፡ በመርካቶ…

Read More

ቢሮው የአገልግሎት አሰጣጡ ዘመናዊ ለማድረግ የሚያግዙ ትላልቅ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ ወደ ተግባር እያሸጋገረ መሆኑ ተገለፀ።

ጥቅምት 28 ቀን 2018 ዓ / ም ፥ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አገልግሎቱን ዘመናዊና ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተገለፀ። በቢሮው የመረጃ ቴክኖሎጂ ማስተዳደር ዳይሬክተር አቶ አብዱላዚዝ ከሊፋ እንደገለፁት በሁሉም ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች የኢፋይሊንግና የኢፔይመንት ቴክኖሎጂ አገልግሎት እንዲስፋፋ በተሰራው ስራ በቴክኖሎጂ መጠቀም ከሚገባቸው ታክስ ከፋዮች መካከል 70 ከመቶ የሚሆኑት ለመጠቀም…

Read More

በግብር ከፋዮች የሚነሱ የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ በተዘጋጀ የ6 ወራት የተከለሰ ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡

የካቲት 14 ቀን 2018ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ዕቅድ በማዘጋጀት ወደ ተግባር ማሸጋገሩ ይታወቃል፡፡ በዛሬው ዕለት ደግሞ ቢሮው ዕቅዱን በመከለሰ ከ7 ሺህ በላይ ከሆኑ ባለሙያዎችና በየደረጃው ከሚገኙ አመራሮች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይት መድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ቢሮው የከተማዋ ኢኮኖሚ የሚያመነጨው…

Read More