ባለፉት 5 ወራት ለግብር ከፋዮች ተገቢው አገልግሎት ባለመስጠት ኃላፊነታቸው ባልተወጡ 179 አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ።

ታህሳስ 11 /2018 ዓ.ም :አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

የቢሮው ሞደርናይዜሽን ዘርፍ በበጀት ዓመቱ 5ወራት ውስጥ በ179 ሰራተኞች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መወሰዱን ገልጿል ።

በቢሮው የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አብዱራህማን በዕቅድ አፈፃፀም ውይይቱ በበጀት ዓመቱ የተሰሩ ስራዎች ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሄዎች እንዲሁም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።

አያይዘውም ከዋና መስራያ ቤት አንስቶ በሁሉም ቅርንጫፎች እና ወረዳዎች ጽህፈት ቤቶች ከሌብነትና ብልሹ አሰራር ፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ ፣ ከስነ_ምግባር አኳያ ክትትልና ድጋፍ በሰርቪላንስ ካሜራ ፣ በምስለ ተገልጋይና በዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ተደርጓልም ብለዋል ።

በዚህም ሃላፊነታቸው በአግባቡ ተወጥተው ባልተገኙ 20 አመራሮችና 159 ፈፃሚዎች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መወሰዱን ገልፀዋል ።

አክለውም በቀጣይ የክትትልና ድጋፍ ስራው የሚቀጥል መሆኑን ጠቁመው በአገልግሎት አሰጣጥ ፣ በሀርሞናይዜሽን ፣ በቲን ቁጥር አሰጣጥ ፣ በኢ_ፋይልና ኢ_ፔመንት ፣ በመዝጊያ ኪሊራንስ እንዲሁም በመማክርት ጉባኤን ውይይት የተጠናከረ ስራዎችን በመስራት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ አሳስበዋል ።

የቢሮው ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ በበኩላቸው የሚሰጡ አገልግሎቶችን የጥራት ደረጃ በማሳደግ ገቢን በፍትሃዊነት መሰብሰብ ይገባል ብለዋል ።

አያይዘውም የከተማዋን የትኩረት ነጥቦችን የጋራ እውቀት በማድረግ አገልግሎት ጠያቂው ካለምንም እንግልት አገልግሎት የሚያገኝበትን ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር በየደረጃው ያለ አመራር ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል ።

ውጤታማ የገቢ አሰባሰብ ለአዲስ አበባ ብልጽግና !

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *