በተቋሙ በየደረጃው ያለው አመራርና ፈፃሚ ኃላፊነቱን በአግባቡ በመወጣት የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች ለመቅረፍ በትኩረት መስራት እንዳለበት ተገለጸ፡፡
ጥቅምት 22 ቀን 2018ዓ.ም፣ አዲስ አበባ ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በማዕከል፣ በሁሉም ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶችና ወረዳዎች ከሚገኙ አመራሮችና ፈፃሚዎች ጋር በአገልግሎት አሰጣጥ የሚስተዋሉ ችግሮች ለመቅረፍ የሚያስችል የውይይት መድረክ በማዕከልና በሁሉም ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶቹ አካሄደ፡፡ በውይይት መድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ተቋሙ ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት በማስፈን ተልዕኮውን በአግባቡ ለመወጣት አዳዲስ አሰራሮችንና…
