የልደታ ክፍለ ከተማ አነስኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ዕለታዊ ደረሰኝ ሳይዙ ልዩ ልዩ ሸቀቶች ከቦታ ቦታ ሲያዘዋውሩ በተገኙ 26 ተሸክርካሪዎች ላይ ቁጥጥር ማድረጉ ገለፀ።

ነሀሴ 26/ 2017 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ወደ ከተማዋ የሚገቡና የሚወጡ እንዲሁም በከተማዋ ከቦታ ወደ ቦታ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ለጫኑት ጭነት ህጋዊ ደረሰኝ ስለመያዛቸው ቁጥጥር የማድረግ ስራ ቀን በቀን ተጠናክሮ ቀጥሏል ። በዛሬው ዕለትም በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የልደታ ክፍለ ከተማ አነስኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በመኪናዎች…

Read More

የቢሮው የሞደርናይዜሽን ዘርፍና የቢሮ ፅ/ቤት በጋራ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የገቢ እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በማካሄድ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎቹን አስቀመጠ ።

ጥቅምት 5 / 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የቢሮው የሞደርናይዜሽንና የፅ/ቤት ዘርፍ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት አቅዶ ያከናወናቸውን ቁልፍ እና አበይት ተግባራት አፈፃፀሙን ገምግሟል ። የግምገማውን መድረክ የመሩት የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መሀመድ አብዱረማንና የፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ ናቸው። በውይይት መድረኩም በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩትን ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ፣…

Read More

ቢሮው ፍትሃዊ የገቢ አሰባሰብን ለማስፈን የሚያደርገው ጥረት ውጤታማነት ለማላቅ የተቋማት ቅንጅት ሊጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ ።

ጥቅምት 20 / 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ቢሮው የበጀት አመቱን የአንደኛ ሩብ አመት የተቋማትና የባለድርሻ አካላት የቅንጅታዊ ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በበጀት ዐመቱ የመጀመሪያው ሩብ አመት ያቀደውን የላቀ ገቢ አሰባሰብ ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅትና ትብብር በማጠናከር ያከናወናቸውን ተግባራት ዛሬ በጥልቀት በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል ።…

Read More

የኢኮኖሚ ነፃነቷን በማረጋገጥ የበለፀገች ሀገር መገንባት የዚህ ትውልድ ተቀዳሚ አጀንዳ ሊሆን እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡

የካቲት 09/2018 ዓ.ም የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች 130ኛው የአድዋ ድል ምክንያት በማድረግ ውይይት አካሄዱ፡፡ የአድዋ እሴት ለሁለንተናዊ ሃገራዊ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚከበረውን የድል በአል አስመልክቶ የተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡ በውይይቱ የፅ/ቤት ኃላፊው አቶ አዳነ ሱሌ አድዋ ዘመን የማይሽረው በደማቅ የተጻፈ የድል ታሪክ፣ ጀግኖች አባቶቻችን ድንበር ተሻጋሪና ለጥቁር ህዝቦች ሁሉ የነጻነት ቀንዲል የሆኑበት፣ ለእኛ ኢትዮጲያውን…

Read More

በመዲናዋ በኤሌክትሮኒከስ ንግድ ላይ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ በተካሄደ የታክስ ኦፕሬሽን በ6 የንግድ ድርጅ

ታህሳስ 25 ቀን 2018ዓ.ም ፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የግብር ስወራን ለመከላከልና የንግድ ሥርዓቱን ፍትሀዊነት ለማረጋገጥና የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተሰራ የተቀናጀና ድንገተኛ ኦፕሬሽን፣ ደረሰኝ ሳይቆርጡ ግብይት ሲፈጽሙ የተገኙ 6 ድርጅቶችንና 9 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዋለ። ቢሮው በዛሬው ዕለት መርካቶን ጨምሮ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በሚሸጡ የንግድ ድርጅቶች ላይ…

Read More

ቢሮው ከንግዱ ማህበረሰብና ከግብር ከፋዮች ጋር ተቀራርቦ በመወያየትና በመስራት በገቢው ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮች ለመፍታት በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡

ህዳር 19/3/2018ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከአዲስ አበባ ከተማ ንግድና ዘርፍ ማሀበራት ም/ቤት የቦርድ አመራሮችና ከ11ንዱም ክፍለ ከተማ የነጋዴ ተወካይ ማህበራት አመራሮች ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱም የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ከገቢዎች ቢሮ ከአገልግሎት አሰጣጥና የግብር ከፋይ መስተንግዶ፣ ከደረሰኝ ባለሙያዎች ቁጥጥርና ስነ ምግባር ፣ ከቀን ገቢ ግምት ፣ ከተሻሻለው…

Read More

ቢሮው የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙን በማጎልበት ፍትሃዊና ዘመናዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለማጎልበት በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ።

የካቲት 11/ 06 / 2018 ዓ / ም የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በየደረጃው ለሚገኙ ባለሙያዎች በሲግታስ (SIGTAS) አተገባበር ላይ ሙያዊ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል። በስልጠና መድረኩ የቢሮው የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ በበጀት ዓመቱ በከተማ ደረጃ 350 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር መግባቱን አስታውሰዋል። አክለውም በበጀት ዓመቱ የታቀደው…

Read More

የቢሮው አመራሮች በከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በመገኘት ቢሮው ለከተማዋ ልማት የሚውል ገቢን በፍትሃዊነት ለመሰብሰብ አቅዶ ወደ ተግባር ያሸጋገራቸው የሪፎርምና የተቋም ግንባታ ስራዎች አተገባበር ምልከታ አካሄዱ፡፡

የካቲት 04 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓትን ለማጎልበት፣ የገቢ መሰረት ለማስፋትና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች ለመቅረፍ የአሰራር፣ የአደረጃጀት፣ የቴክኖሎጂ ልማትና የሰው ሀብት ልማት የሪፎርም ተግባራት ለይቶ ወደ ተግባር ማሸጋገሩ ይታወቃል፡፡ በቢሮው በጥናት ተለይተው ወደ ተግባር የተሸጋገሩ የሪፎርም ተግባራት ለከተማዋ ሁለንተናዊ ልማት…

Read More

የፈረንሳይ የልማት ድርጅት(AFD) ለገቢዎች ቢሮ በንብረት ታክስ (Property tax) አተገባበር ላይ ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገለፀ፡፡

መስከረም 26 ቀን 2018ዓ.ም ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት ልዑካን ቡድን ጋር በንብረት ታክስ አስተዳደር፣ የትግበራ ሂደትና ድጋፍ ላይ ውይይት አካሄደ፡፡ በውይይቱ የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ የከተማ አስተዳደሩ ባለፉት 5 ዓመታት በገቢ ዘርፉ ተጨባጭ ለውጦችን ለማስመዝገብ መቻሉን ለልዑካን ቡድኑ ገልፀዋል፡፡ በዚህም በ2010 ዓ.ም በከተማ አስተዳደደሩ…

Read More

ቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ተሳትፎና በአመራሮቿ ቁርጠኛነት አቋም የታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ እንዳስደሰታቸው ገለፁ፡፡

መስከረም 5/ 2015 ዓ. ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ” የህዳሴ ግድባችን የኢትዮጵያ ማንሰራራት ብስራት ነው ” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄዷል ። በውይይት መድረኩ የታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን ከፍታ ከማሳየቱ ባሻገር የብሔራዊ መግባባት እና አንድነትን የሚያሳይ መሆኑ ተገልፆል፡፡ የውይይቱን መድረክ የከፈቱት…

Read More