“ወደ ከተማ የሚገቡ ፣የሚወጡ እንዲሁም ከተማ ውስጥ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ማንኛውም ደረቅ ጭነትና የተለያዩ ሸቀጣ ሸቀጦች የጫኑ ተሽከርካሪዎች ደረሰኝ ስለመያዛቸው ቁጥጥር እያደረግን ነው”- ገቢዎች ቢሮ
ነሀሴ 24 ቀን 2017ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በሁሉም የከተማዋ አቅጣጫዎች ወደከተማዋ የሚገቡ፣ከከተማዋ የሚወጡና በከተማዋ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ፣ሚኒባሶችና ኣነስተኛ ሽፍን መኪኖች ላይ የመኪና ኦፕሬሽን ስራዎች እያከናወነ መሆኑን አሳውቋል። ቢሮው እያካሄደ ያለው የመኪና ኦፕሬሽን ስራ ተሽከርካሪዎቹ ጭነው የሚንቀሳቀሱት ልዩ ልዩ ሸቀጦች፣ምርቶችና የኮንስትራክሽን ግብአቶች በህጋዊ ግብይት በደረሰኝ የተፈፀሙ ስለመሆናቸው…
