ቢሮው የቁጥጥር ስርዓቱ በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ ባርኮድ የተካተተበት የመታወቂያ ካርድ ማዘጋጀቱ ግልፀኝነት የተላበሰ የቁጥጥር ስርዓት ለመዘርጋት ያለው ቁርጠኛነት ማሳያ ነው ሲሉ ያነጋገርናቸው የመርካቶ ነጋዴዎች ገለጹ

ነሐሴ 07 / 2017 ዓ / ም የአዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በከተማዋ እያካሄደ የሚገኘውን የቁጥጥር ሾል በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በማድረግ ከብልሹ አሰራር ለመከላከል የሚያስችል አሠራር መዘርጋቱን በትላንቱ ዕለት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡ የዝግጅት ክፍላችንም በዛሬው ዕለት በመርካቶ አካባቢ በመገኘት የንግዱ ማህበረሰብን ቢሮው ወደ ተግባር ባሸጋገር በቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ስርዓት ላይ ያላቸውን…

Read More

ቢሮው በ2018 በጀት አመት የሌብነትና ብልሹ አሰራር ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች በመቅረፍና የተጠያቂነት አሰራር በማጠናከር የታክስ ፍትሃዊነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ ተገለፀ፡፡

ነሐሴ 10 / 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዋና መስሪያ ቤቱ ፣ በ17ቱ ቅርንጫፎችና በወረዳ ካሉ ከ 7ሺህ በላይ ከሆኑ አመራሮችና ሰራተኞችጋር በመልካም አስተዳደር፣ በአግልግሎት አሰጣጥና በሌብነትና ብልሹ አሰራር ዙሪያ ውይይት አካሂዷ፡፡ በውይይቱ የቪዲዮ ገለፃ ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ አቶ ቢንያም ምክሩ በ2018 በጀት…

Read More

በመዲናዋ በሱፍ ልብስ ንግድ ስራ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲፈፅሙ የተገኙ 7 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

የካቲት 15 ቀን 2018ዓ.ም ፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የግብር ስወራን ለመከላከልና የንግድ ሥርዓቱን ፍትሀዊነት ለማረጋገጥና የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተከናወነ የተጠና፣ የተቀናጀና ድንገተኛ ኦፕሬሽን በ5 የሱፍ ልብስ ንግድ ድርጅቶች ደረሰኝ ሳይቆርጡ ግብይት ሲፈጽሙ የተገኙ 7 ተጠርጣሪዎችን በህግ ቁጥጥር ሾር ማዋሉን አሳወቀ። ቢሮው የካቲት 14 ቀን 2018ዓ.ም በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች…

Read More

ዜና ትንታኔ

========= በገቢ አሰባሰቡ ላይ የታየው ሁሉን አቀፍ እድገትና እምርታ በቀጣይም በ2018 በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ፡፡ ጳጉሜ 03 / 2017 ዓ / ም ፣ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የከተማው ማህበረሰብ የመልማት ፍላጎት የመመለስ ትልቅ ኃላፊነት ወስዶ እየተጋ የሚገኝ ተቋም ነው ፡፡ በዚህም ምክንያት ቢሮው እያከናወናቸው በሚገኙ ተግባራት የተነሳ የገቢ…

Read More

በቢሮው የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማጎልበት በአገልግሎት አሰጣጥ የሚስተዋሉ ችግሮች ለመቅረፍ በሚደረጉ ጥረቶች የመጡ ለውጦች ቀጣይነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ያነጋገርናቸው ግብር ከፋዮች ገለፁ ።

ጥር 28 / 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የቢሮ አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን በአዲስ አበባ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች እና በአዲስ አበባ ቁጥር 2 መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ሲገለገሉ ያገኘናቸው ግብር ከፋዮች ገለጹ። ቢሮው በቅርቡ የጀመራቸው የሪፎርም ስራዎች እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ለለውጡ ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን አስተያየት ሰጪዎቹ ጠቁመዋል። በከተማዋ…

Read More

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር ችግኝ ተከላ አካሄደ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር ችግኝ ተከላ አካሄደ። ሐምሌ 24-2017 ዓ /ም የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ መርሐግብሩ የተካሄደው በአዲስ ከተማና በለሚኩራ ክፍለ ከተሞች ሲሆን በመርሐግብሩ የቢሮው ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀንበር 700 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል…

Read More

በመዲናዋ ባለፉት አራት ወራት ከ5 ሺህ በላይ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የደረሰኝ ቁጥጥር በመካሄድ ከ954 ሚሊዮን ብር በላይ ደረሰኝ እንዲቆረጥ መደረጉ ተገለፀ።

ህዳር 17 ቀን፤2018፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት አራት ወራት በ5 ሺህ 203 የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪዎች ላይ የደረሰኝ ቁጥጥር ማካሄዱ ተገልፆል፡፡ የደረሰኝ ቁጥጥሩ በሁሉም የከተማዋ አቅጣጫዎች ወደ ከተማዋ በሚገቡ፣ከከተማዋ በሚወጡና በከተማዋ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ፣ሚኒባሶችና አነስተኛ ሽፍን መኪኖች ላይ ነው የተካሄደው፡፡ በዚህም ያለደረሰኝ ጭነት በመያዝ ሲንቀሳቀሱ…

Read More

በቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ በፊት ከሚደርስባቸው ማጭበርበር እንደታደጋቸው በመርካቶ ያነጋገርናቸው ግብር ከፋዮች አሳወቁ ።

ነሐሴ 12 / 2017 ዓ / ም የአዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የቁጥጥር ስራው በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በማድረግ ወደ ተግባር ማሸጋገሩ ይታወቃል ። የኮሙንኬሽን የዝግጅት ክፍላችን በመርካቶ አካባቢ ዛሬም በመዘዋወር ቢሮው ወደ ተግባር ባሸጋገረው በቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ስርዓት ላይ ያለውን ሂደት የታክስ ( ግብር ) ከፋዮች አስተያየት ቅኝት አድርጓል ፡፡ በመርካቶ…

Read More

የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች 18ኛውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን‹‹ ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጲያ ሕዳሴ›› በሚል መረ ቃል አከበሩ፡፡

ጥቅምት 3/2018ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በዛሬው ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከበረውን 18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የብሄራዊ መዝሙር በመዘመርና ቃለ መሀላ በመፈፀም ሥነ-ሥርዓት እንዲሁም በተለያዩ ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ አክብረው ውለዋል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳኔ ሱሌ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን የምናከብረው በእኛ ኢትዮጵያውያን…

Read More

ቢሮው ለወረዳ ማይክሮ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት አመራሮች በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ ላይ የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠና ሰጠ።

ህዳር 1 ቀን 2018ዓም፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከኔዘርላንድ የልማት ድርጅት ጋር በመተባበር በስሩ ለሚገኙ የወረዳ ማይክሮ ቅ/ፅ/ቤት አመራሮች በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ 1395/2017 ላይ ስልጠና ሰጥቷል። የስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የቢሮው የታክስ ጉዳዮች ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሎ ወርቅነሽ ሰቦቃ ቢሮው በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች አቅም ለመገንባት የሚያስችሉ ተግባራት በተከታታይነት እያከናወነ ይገኛል…

Read More