የዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ባለሙያዎች ፈጣንና ጥራት ያለው መረጃ በአግባቡ በማደራጀትና ለተቋም አመራሮች በማቅረብ ትክክለኛ ውሳኔ እንዲወሰን የማድረግ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባቸው ተገለፀ፡፡
መስከረም 9 ቀን 2017ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ለቅርንጫፍ ፅ/ቤት የበጀትና ዕቅድ ክትትልና ድጋፍ የስራ ሂደቶችና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል፡፡ የስልጠና መድረኩን የከፈቱት የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በየደረጃው ያለው የእቅድ ክፍል ጥራት ያለው፣ ፈጣንና በአግባቡ የተደራጀና የተተነተነ መረጃ ለውሳኔ በማቅረብ የተቋሙ ዕቅድ እንዲሳካ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ ከትክክለኛና…
