ቢሮው ያቀረብነውን የታክስ ቅሬታ በአግባቡ በመመርመር ፍትሀዊ የሆነ የታክስ ውሳኔ ማሻሻያ አድርጎልናል፡፡›› አቶ ብሩክ ተገኝ

ነሀሴ 30 / 2017 ዓ.ም ፡ አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ያቀረብነውን የታክስ ቅሬታ በአግባቡ በመመርመር ፍትሀዊ የሆነ የታክስ ውሳኔ ማሻሻያ አድርጎልናል ሲሉ ከዝግጅታችን ክፍል ጋር ቆይታ ያደረጉት በዚጊዛግ ሆቴልና እስፖ ድርጅት ዋና ሾል አስኪያጅ አቶ ብሩክ ተገኝ ገልፀውልናል ። ድርጅታቸው ከዚህ በፊት እንደዚህ አይነት የታክስ ውሳኔ ደርሷቸው የማያውቅ መሆኑን…

Read More

የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች 18ኛውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን‹‹ ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጲያ ሕዳሴ›› በሚል መረ ቃል አከበሩ፡፡

ጥቅምት 3/2018ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በዛሬው ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከበረውን 18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የብሄራዊ መዝሙር በመዘመርና ቃለ መሀላ በመፈፀም ሥነ-ሥርዓት እንዲሁም በተለያዩ ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ አክብረው ውለዋል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳኔ ሱሌ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን የምናከብረው በእኛ ኢትዮጵያውያን…

Read More

የቢሮው የሞደርናይዜሽን ዘርፍና የቢሮ ፅ/ቤት በጋራ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የገቢ እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በማካሄድ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎቹን አስቀመጠ ።

ጥቅምት 5 / 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የቢሮው የሞደርናይዜሽንና የፅ/ቤት ዘርፍ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት አቅዶ ያከናወናቸውን ቁልፍ እና አበይት ተግባራት አፈፃፀሙን ገምግሟል ። የግምገማውን መድረክ የመሩት የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መሀመድ አብዱረማንና የፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ ናቸው። በውይይት መድረኩም በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩትን ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ፣…

Read More

የፈረንሳይ የልማት ድርጅት(AFD) ለገቢዎች ቢሮ በንብረት ታክስ (Property tax) አተገባበር ላይ ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገለፀ፡፡

መስከረም 26 ቀን 2018ዓ.ም ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት ልዑካን ቡድን ጋር በንብረት ታክስ አስተዳደር፣ የትግበራ ሂደትና ድጋፍ ላይ ውይይት አካሄደ፡፡ በውይይቱ የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ የከተማ አስተዳደሩ ባለፉት 5 ዓመታት በገቢ ዘርፉ ተጨባጭ ለውጦችን ለማስመዝገብ መቻሉን ለልዑካን ቡድኑ ገልፀዋል፡፡ በዚህም በ2010 ዓ.ም በከተማ አስተዳደደሩ…

Read More

ቢሮው የቁጥጥር ስራው በቴክኖሎጂ ማስደገፉ ስራቸውን በኃላፊነት ስሜት እንዲሰሩ ያስቻላቸው መሆኑን የመርካቶ ነጋዴዎች ገለፁ።

መስከረም 21 / 2018 የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ቢሮው የቁጥጥር ስራው በቴክኖሎጂ ማስደገፉ በታክስ ከፋዩ ሕብረተሰብ ዘንድ የፈጠሩት ስሜት በሚመለከት የመርካቶ ነጋዴዎችን አነጋግሯል። በመርካቶ በጨርቃጨርቅ ዘርፍ ላይ ተሰማሩት የሚሰሩት አቶ ዋቢ ግርግር እና አቶ አስፋው ሐይሌ እንደገለጹት እንደከተማ በከፈሉት ግብር የተሰሩ የልማት ስራዎች ሲያዩ ከፍተኛ የሆነ ደስታ የሚሰማቸው በመግለጽ…

Read More

የዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ባለሙያዎች ፈጣንና ጥራት ያለው መረጃ በአግባቡ በማደራጀትና ለተቋም አመራሮች በማቅረብ ትክክለኛ ውሳኔ እንዲወሰን የማድረግ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባቸው ተገለፀ፡፡

መስከረም 9 ቀን 2017ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ለቅርንጫፍ ፅ/ቤት የበጀትና ዕቅድ ክትትልና ድጋፍ የስራ ሂደቶችና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል፡፡ የስልጠና መድረኩን የከፈቱት የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በየደረጃው ያለው የእቅድ ክፍል ጥራት ያለው፣ ፈጣንና በአግባቡ የተደራጀና የተተነተነ መረጃ ለውሳኔ በማቅረብ የተቋሙ ዕቅድ እንዲሳካ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ ከትክክለኛና…

Read More

የሐዋሳ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ልዑካን ቡድን አባላት ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለመዘርጋት እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ላይ የልምድ ልውውጥ አካሄዱ፡፡

መስከረም 10/ 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የሐዋሳ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በቢሮው በመገኘት ቢሮው የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን ቀልጣፋ ፣ ውጤታማ ፣ ከሙስና የፀዳ እና ግቡን ያሳካ እንዲሆን የዘረጋቸው አሰራሮች እና ስትራቴጂዎች ዙሪያ የልምድ ልውውጥ አካሂዷል ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ለቡድኑ የእንኳን ደህና መጣችሁ…

Read More

ቢሮው በቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ስራ መስራቱ ሕጋዊውና ሕገወጡን በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሆኑን ያነጋገርናቸው ነጋዴዎች ገለጹ ፡፡

ነሐሴ 13 / 2017 ዓ / ም የአዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የቁጥጥር ስራው በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ ማድረጉ ሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን ከመከላከልና የአሰራር ግልጽነት ከመፍጠሩም ባሻገር ሕጋዊውና ሕገወጡን በቀላሉ መለየት የሚያስችል በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በመርካቶ በመደብራቸው ሲሰሊ ያገኘናቸው ነጋዴዎች ገለጹ ፡፡ የዝግጅት ክፍላችን በመርካቶ አካባቢ በመዘዋወር ቢሮው ወደ ተግባር ባሸጋገር…

Read More

የቢሮው የታክስ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የገቢ እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በማካሄድ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎቹን አስቀመጠ ።

ጥቅምት 5 / 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የቢሮው የታክስ ዘርፍ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት አቅዶ ያከናወናቸውን ቁልፍ እና አበይት ተግባራት አፈፃፀሙን ገምግሟል ። የግምገማውን መድረክ የከፈቱት በቢሮው የታክስ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ ሎ ወርቅነሽ ሰቦቃ ግምገማው በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩትን ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ፣ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎች እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት…

Read More

በቢሮው የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባዔ ተቋቋመ ።

ጥቅምት 15 / 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በሚሠጠው አገልግሎት እርካታን ማረጋገጥ ይቻል ዘንድ የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባዔን በዛሬው ዕለት አቋቁሟል። በዚህ የመማክርት ጉባኤ ምስረታ ላይ 50 የሚሆኑ ከንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፣ ከሲቪክ ማህበራት፣ ከንግድ ማህበረሰብ ፣ ከተገልጋይ ፣ ከባለድርሻ አካላት ሴክተር ተቋማት ፣ ከገቢዎች…

Read More